የሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት/North shoa zone high court/

የሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት/North shoa zone high court/ ይህ ፔጅ በአብክመ ጠቅላይ ፍ/ቤት የሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት የሚያከናዉናቸዉን የዳኝነት ስራዎችና ሌሎች የአስተዳደር ስራዎችን ለህዝብ የሚያሳዉቅበት ነዉ

በሰሜን ሽዋ ዞን የደ/ብርሃን ሪጅኦ ፖሊታን በሚገኙ ቀበሌዎች የባህል ፍርድ ቤት ዳኞችን ማስመረጥ ተጠናክሮ ቀጥሏል ሰኔ 15/2018 ዓ.ም (ደ/ብርሃን)በሰሜን ሽዋ ዞን የደ/ብርሃን ሪጅኦ ፖ...
22/06/2026

በሰሜን ሽዋ ዞን የደ/ብርሃን ሪጅኦ ፖሊታን በሚገኙ ቀበሌዎች የባህል ፍርድ ቤት ዳኞችን ማስመረጥ ተጠናክሮ ቀጥሏል
ሰኔ 15/2018 ዓ.ም (ደ/ብርሃን)
በሰሜን ሽዋ ዞን የደ/ብርሃን ሪጅኦ ፖሊታን በሚገኙ ቀበሌዎች የባህል ፍርድ ቤት ዳኞችን የማስመረጥ ስራው ተጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን በትናትናው እለት ከ20 ቀበሌዎች በላይ የባህል ፍርድ ቤት ዳኞች ሲመረጥ ውሏል፡፡ ምርጫ ከተደረገባቸው ቀበሌዎች ውስጥ በ3 ቀበሌዎች ላይ የሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ክቡር አቶ ዮሐንስ ወንድሙ በመገኘት ምርጫውን በማስመረጥና በማስተባበር ውለዋል፡፡
እንደ አጠቃላይ በደ/ብርሃን ከተማ 39 ቀበሌዎች ያሉ ሲሆን አሁን ላይ በ29 ቀበሌዎች ላይ የባህል ፍርድ ቤት ዳኞች ተመርጠዋል፡፡ በቀሪዎቹ 10 ቀበሌዎች ላይ በቀጣይ ጊዜያት ለማጠናቀቅና ለተመረጡ የባህል ፍርድ ቤት ዳኞችም ስልጠና ለመስጠት ልዩ ልዩ ተግባራት እየተከናወነ ይገኛል፡፡

20/06/2026
በደ/ብርሃን ሪጅኦ ፖሊታን በአጼ ዘርያቆብ ክፍለ ከተማ ኃይለ ማርያም ማሞ ቀበሌ የባህል ፍርድ ቤት ዳኞችን  አስመረጠ ።ደ/ብርሃን፡- ሰኔ 10/2018 ዓ.ም (ሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ...
17/06/2026

በደ/ብርሃን ሪጅኦ ፖሊታን በአጼ ዘርያቆብ ክፍለ ከተማ ኃይለ ማርያም ማሞ ቀበሌ የባህል ፍርድ ቤት ዳኞችን አስመረጠ ።
ደ/ብርሃን፡- ሰኔ 10/2018 ዓ.ም (ሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት)
በዛሬው በአጼ ዘርያቆብ ክፍለ ከተማ ኃይለ ማርያም ማሞ ቀበሌ የባህል ፍርድ ቤት ዳኞችን ለማስመረጥ በተዘጋጀ መድረክ ላይ የተገኙት የሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ክቡር አቶ ዮሐንስ ወንድሙ የደ/ብርሃን ከተማ ባህልና ቱሪዝም ኃላፊ አቶ ተክሌ ኃ/ሚካኤል እና የሀይለ ማርያም ማሞ ቀበሌ አስተዳዳሪ አቶ አላዛር ንጉሴ በተገኙበት የባህል ፍርድ ቤት ዳኞችን አስመርጠዋል፡፡
ቀበሌው የባህል ፍርድ ቤት ዳኞች ለማስመረጥ ያለው ተነሳሽነትና ለጉዳዩ ልዩ ትኩረት በመስጠት በእለቱ ለተገኙት እንግዶችና ተሰብሳቢዎች የቀበሌውን የባህል ባንድ በመጋበዝ አቀባበል አድርገዋል፡፡ በመቀጠልም የእለቱን ፕሮግራም የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ክቡር አቶ ዮሐንስ ወንድሙ እንደገለጹት ህብረተሰቡን በቅርበት ለማገልገል የባህል ፍ/ቤት ሽማግሌዎች ለማስመረጥ በአዋጅ ቁጥር 298/2017 ዓ.ም የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት የባህል ፍ/ቤቶችን ለማቋቋምና ይህንኑ አዋጅ ለማስተግበር በመጣው መመሪያ ቁጥር 23/2018 ዓ.ም በመተግበር ላይ እንደሚገኝ ገልጸው የባህላዊ ፍ/ቤቶች መቋቋም ዋነኛ የማህበረሰብን የባህል፣ ህግና እሴቶች መሰረት በማድረግ አለመግባባቶች በአቅራቢያቸው በመፍታት ተደራሽነትን፣ወጭን፣ጊዜን በመቆጠብ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ከፍተኛ ሚና ይጫወታል ሲሉ ገልጸዋል።
አክለውም የባህል ፍርድ ቤት ሽማግሌዎች ለፍትህና ለእውነት ለህሊናቸው በመቆም ለቀበሌው ህዝብ ፍትሃዊ የሆነ የሽምግልና ስርዓት የሚያከናውኑ መሆን አለባቸው ብለዋል፡፡
የባህልና ቱሪዝም ኃላፊው እንደገለፁት የባህል ፍ/ቤት ዳኞች ሲያስመርጡ ማህበረሰቡ እርስ በእርሱ የሚተዳደርበት የሽምግልና ሥርዓትን ተከትለው የሚዳኙ አካላትን እንዲመረጡ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በመቀጠልም ክቡር ፕሬዚዳንቱ የባህልና ቱሪዝም ኃላፊውና የቀበሌው አስተዳዳሪ በጋራ 10 ጥቆማዎችን ተቀብለው ከነዚህ ውስጥ ባህሉን አውቀውና ጠብቀው የሚሰሩ፣በማህበረሰቡ ዘንድ ቅቡልነት ያላቸውን፣ በስነ-ምግባራቸው መልካም የሚባሉትን በድምጽ ብልጫ ተለይተው 5 የባህል ዳኞችን አስመርጠዋል፡፡

የሰሜን ሸዋ ዞን የዳኝነት እና የፍትህ አካላት የትብብር መድረክ የ11 ወር አፈፃፀም ገመገመደ/ብርሃን፣ ሰኔ 08/2018 ዓ/ም (ሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት)የሰሜን ሸዋ ዞን የዳኝነት...
15/06/2026

የሰሜን ሸዋ ዞን የዳኝነት እና የፍትህ አካላት የትብብር መድረክ የ11 ወር አፈፃፀም ገመገመ
ደ/ብርሃን፣ ሰኔ 08/2018 ዓ/ም (ሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት)
የሰሜን ሸዋ ዞን የዳኝነትና የፍትህ አካላት የትብብር መድረክ አብይ ኮሚቴና የቴክኒክ ኮሚቴ የ2018 በጀት አመት የ11 ወራት እቅድ አፈፃፀም ገምግመዋል፡፡ በግምገማው ላይ ሁሉም አባል ተቋማት ሀላፊዎች የተገኙ ሲሆን ግምገማውን ያስጀመሩት የሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት እና የአብይ ኮሚቴ ሰብሳቢ ክቡር አቶ ዮሐንስ ወንድሙ የፍትህ ተቋማት ለፍትህ መረጋገጥ ያለው አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑን ገልፀው በ2018 በጀት አመት 11 ወራት የተከናወኑትን ዋና ዋና ተግባራት በሪፖርት ይቀርባል ብለዋል፡፡
ሪፖርቱንም ያቀረቡት የሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የወንጀል ዳኝነት አገልግሎት አሰጠጥ ቡድን መሪና የቴክኒክ ኮሚቴው ሰብሳቢ ክቡር አቶ ቦጋለ ጌታቸው ሪፖርቱን አቅርበዋል፡፡
የቴክኒክ ኮሚቴዉ በ2018 ዓ/ም 11 ግቦችንና 49 የሚደርሱ ተግባራትን ያካተተ ሰፊ እቅድ አቅዶ ወደ ተግባር የገባ ሲሆን ስራዎችን በየጊዜዉ እተገናኘ ሲገመግም የቆየ ሲሆን በ11 ወር ዉስጥ ኮሚቴዉ የሰራቸዉን ስራዎች በጥንካሬና በክፍተት በታዩ ጉዳዮች አንስቶ ሰፊና ጥልቅ ግምገማ አድርገዋል፡፡
‎በሪፖርቱ የቀረቡት ጠንካራ አፈጻጸሞች ተናቦና በጋራ በቅንጅት በመሰራት የመጣ ዉጤት መሆኑን አንስተዉ የሙያ ነጻነትን ሳይነካ ሁሉም ተቋማት በጋራ ሊያሰሯቸዉ በሚችሉ ተመጋጋቢ ስራዎች ትኩረት አድርገዉ መስራት ያለባቸዉ መሆኑን አንስተዋል በቀጣይም በተስተዋሉ ክፍተቶ ላይ ልዩ ትኩረት በመስጠት መሰራት አለባቸው ያላቸውን ተግባራት በትኩረት አቅጣጫቸው ላይ በማስቀመጥ ግምገማውን አጠቃለዋል፡፡

የመርሀቤቴ እና አጎራባች ወረዳ ፍርድ ቤቶች  ባዘጋጁት መድረክ የከፍተኛ ፍርድ ቤቱ ፕሬዚዳንትና የዳኞች አስተዳደር ንዑስ ጉባኤ ጽ/ቤት ኃላፊ በመሳተፍ ውይይት አደረጉ       ደ/ብርሃን፣ ...
13/06/2026

የመርሀቤቴ እና አጎራባች ወረዳ ፍርድ ቤቶች ባዘጋጁት መድረክ የከፍተኛ ፍርድ ቤቱ ፕሬዚዳንትና የዳኞች አስተዳደር ንዑስ ጉባኤ ጽ/ቤት ኃላፊ በመሳተፍ ውይይት አደረጉ
ደ/ብርሃን፣ ሰኔ 06/2018 ዓ/ም (ሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት)
የመርሀቤቴ እና አጎራባች 4 ወረዳ ፍርድ ቤቶች ባመቻቹት መድረክ ላይ የሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ክቡር አቶ ዮሐንስ ወንድሙ እና የዳኞች አስተዳደር ንዑስ ጉባኤ ጽ/ቤት ኃላፊ ክቡት አቶ ይርጋ ደጀኔ በቨርችዋል በመሳተፍ ውይይት አደረጉ፡፡ ውይይት የተደረገባቸው ጉዳዮችም በተለይ በቀሪው አጭር የበጀት አመቱ ማጠናቀቂያ ጊዜ ላይ ልዩ ትኩረት በያስፈልጋቸው ጉዳዮች ላይ የተወያዩ ሲሆን ይኸውም በመዛግብት አፈፃፀም ላይ፣ በባህል ፍርድ ቤቶች አደረጃጀት፣ በስነ-ምግባርና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል፡፡

የደብረ ብርሃን ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት በአገልግሎት አሰጣጥና ቅሬታ አፈታት ዙሪያ ስልጠና ሰጠ       ደ/ብርሃን፣ ሰኔ 06/2018 ዓ/ም (ሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት)የደብረ ብርሃ...
13/06/2026

የደብረ ብርሃን ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት በአገልግሎት አሰጣጥና ቅሬታ አፈታት ዙሪያ ስልጠና ሰጠ
ደ/ብርሃን፣ ሰኔ 06/2018 ዓ/ም (ሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት)
የደብረ ብርሃን ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት ለዳኞች፣ የጉባኤ ተሿሚዎችና ለአስተዳደር ሰራተኞች በዛሬው እለት በጫጫ ከተማ በአገልግሎት አሰጣጥና ቅሬታት አፈታት ላይ ስልጠና ሰጥቷል፡፡ በስልጠና ላይ የሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ክቡር አቶ ዮሐንስ ወንድሙ፣ የከፍተኛ ፍርድ ቤቱ የማናጅመንት አባላት፣ የጫጫ ከተማ አስተዳዳሪ አቶ ደረሰ ደመመ ተገኝተዋል፡፡
በስልጠና ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ዮሐንስ ወንድሙ ስልጠናውን አስመልክቶ ለሰልጣኞች መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን በመልዕክታቸውም ተቋማት ተቀናጅተው ለባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠታቸው ለውጤታማ የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጥ ያለው አበርክቶ ቀላል አይደለም ብለዋል ይህንንም ስልጠና ያዘጋጁትን አካላት አመስግነዋል፡፡
ሌላው በስልጠናው ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የአንጎለላ እና ጠራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ደረሰ ደመመ ባለፈው በጀት አመት የዳኝነት የሚሰጥበት እና ህዝብ የሚገለገልበት ተቋም የዳኝነት ስራውንና ህዝቡን የሚመጥን ቢሮ ባለመሆኑ በጀቱን የከተማው አስተዳደር በመቻል በ90 ቀናት ቢሮ አስገንብተን ምቹና ውብ የሆነ የችሎት አዳራሽ አሰርተን ለፍርድ ቤቱ ያስረከብን መሆኑይ ታወቃል፡፡ ይህ መደረጉ የወረዳችን ማህበረሰብ በተሻለ ቢሮ እንዲስተናገድ ጥሩ መደላድል ፈጥሯል ብለዋል፡፡ በቀጣይም ይህንን ስራዎችን አጠናክረን እናስቀጠለለን ብለዋል፡፡
የእለቱን ስልጠና የሰጡት የሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኞች አስተዳደር ንዑስ ጉባኤ ፅ/ቤት ኃላፊ ክቡር አቶ ይርጋ ደጀኔ በአገልግሎት አሰጣጥና ቅሬታ አፈታት ላይ የስልጠና ሰነድ በማዘጋጀት አሰልጥነዋል፡፡
ከስልጠናው በኋላም ሰልጣኞችን ክቡር ፕሬዚዳንቱ ያወዩ ሲሆን ከስልጠናው በተገኘው ግብአት ወደ ተቋማችን የሚመጡ ማህበረሰብ በመልካም ስነ-ምግባር በታማኝነትና በቅንነት ማገልገል አለብን ሲሉ አስሳበዋል ሌላው በሚስተዋሉ ክፍተቶችም ላይ ሰፊ ውይይት አድርገዋል ከሰልጣኞችም በርካታ በስራ ላይ ያጋጠሟቸውን ችግሮች አንስተው ምላሽና ማብራሪያ ክቡር ፕሬዚዳንቱ ሰጥተዋል በቀጣይም መሰራት ያለባቸውን ሁሉም ሀላፊነትን ወስዶ መስራት እንዳለባቸውም ጭምር አሳስበዋል፡፡
ስልጠናው በሰልጣኞች ላይ ከፍተኛ የሆነ መነቃቃት የፈጠረ እና ወደፊትም እንደዚህ ያሉ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች ቢሰጡ ቀልጣፋ፣ ተደራሽ፣ ተገማች እና የሕዝብ አመኔታ ያተረፈ አግልግሎት ለማህበረሰቡ ለመስጠት እንደሚያስችል ሰልጣኞች አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡

የሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የ11 ወራት እቅድ አፈፃፀም ገመገመደ/ብርሃን ሰኔ 04/2018 ዓ.ም /ሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት/በዛሬው እለት የሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤ...
12/06/2026

የሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የ11 ወራት እቅድ አፈፃፀም ገመገመ

ደ/ብርሃን ሰኔ 04/2018 ዓ.ም /ሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት/

በዛሬው እለት የሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የማኔጅመንት አባላት የ2018 በጀት ዓመት የ11 ወራት የተቋሙን አጠቃላይ የስራ አፈፃፀም ገምግመዋል።

አጠቃላይ የተቋሙን ሪፖርት ያቀረቡት የከፍተኛ ፍርድ ቤቱ የእቅድ በጀት ክትትልና ግምገማ ባለሙያ አቶ ሸጋው ወ/ጊዮርጊስ የ11 ወር የመዝገቦች አፈፃፀም በዝርዝር ለማናጅመንት አባላቱ አቅርበዋል። ከቀረበዉ ሪፖርት ላይ በመነሳት በጥልቀት ከገመገሙ በሗላ በጥንካሬ የተከናወኑ ተግባራትን በማስቀጠል በክፍተት የታዩትንና የእቅዳችን አካል የሆኑትን በቀሪዎቹ አጭር ቀናት ውስጥ በቅንጅት መፈፀም አለብን ሲሉ የከፍተኛው ፍርድ ቤት ፕሬዘዳንት ክቡር አቶ ዮሐንስ ወንድሙ በማጠቃለያቸው ላይ አሳስበዋል።

12/06/2026

Address

Debre Birhan

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት/North shoa zone high court/ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share