Konjit Legal Clinic

Konjit Legal Clinic በሕግ ዙሪያ ያለንን ግንዛቤ ለማስፋት እንዲሁም ሀሳቦችን ለመለዋወጥ

16/01/2026

የፌደራል የገቢ ግብር አዋጅ ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 1395/2017 አስመልክቶ አጭር ማብራርያ

 ማሻሻያ አዋጁ ከሐምሌ 1 ቀን 2017ዓም ስራ ላይ ዉሏል።
በአዋጁ በግብር ስርዓቱ ላይ በርካታ ማሻሻያዎች እንዲሁም አዳዲስ የታክስ አሰባሰብ ስርዓቶችን ያካተተ ነዉ። ለአብነት ያህልም፡-
 አዲስ የግብር ከፋይ ደረጃዎች
በቀድሞ ሶስት የግብር ከፋይ ደረጃዎች ሀ፣ ለ ፣ሐ ቀርቶ ሁለት ደረጃዎች
ሀ እና ለ ብቻ እንዲሆን ተደርጓል።
ደረጃ 'ሀ' ግብር ከፋይ ድርጅቶች እና ጠቅላላ ዓመታዊ ገቢዉ ብር 2 ሚሊዮን ወይም ከዚያ በይ የሆነ ማንኛዉም ሰዉ እንዲሁም ደረጃ 'ለ' ግብር ከፋይ ድርጅትን ሳይጨምር መታዊ ገቢዉ ከብር 2 ሚሊዮን የሚያንስ ሰዉ ሲሆን ሌላዉ አዋጁ ያካተተዉ ግብር የተጣለበት ገቢ
 ከዲጂታል አገልግሎትና ዲጂታል ይዘት ፈጠራ የሚገኝ ገቢ ሲሆን ከዲጂታል አገልግሎት (የሳተላይት ቴሌቭዥን፣የሶፍት ዌር አቅርቦት ወዘተ..)በመስጠት የሚገኝ ገቢ 5% ግብር የሚከፍልበት እና ከዲጅታል ይዘት ፈጠራ ( ከዩቲዩብ፤ከቪዲዮ ማጋርያ መድረኮች ፣ከፖድካስትና መሰል የማህበራዊ መድረኮች) የሚገኝ ገቢ በመደበኛ የንግድ እንቅስቃሴ አካል ከሆነ የንግድ ገቢ ግብር የተጣለበት ሲሆን ከዚህ ዉጭ ከሆነ ሌሎች ገቢዎች በሚል ተካቶ 15%ግብር ይከፈልበታል።
 በጥሬ ገንዘብ ግብይት ላይ ገደብ መጣል
ማንኛዉም ግብር ከፋይ በአንድ ግብይት ከብር 50,000 በላይ በጥሬ ገንዘብ መቀበል ወይም መክፈል እንደማይችል ተደንግጓል።
ይቀጥላል........

https://youtube.com/shorts/Xolv0zjIfMw?feature=share
01/01/2026

https://youtube.com/shorts/Xolv0zjIfMw?feature=share

ጠቃሚ የታክስ ህግ መረጃዎች እና ማብራሪያዎች በሙያዉ የዳበረ እዉቀትና ልምድ ባላቸዉ ባለሙያዎች የሚቀርብበት መድረክ ነዉ፡፡

22/08/2025

የገቢ ግብር ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 1395/2017

በምክር ቤት ከጸደቀበት ሐምሌ 1/2017 ዓም ጀምሮ በስራ ላይ በዋለዉ የገቢ ግብር ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 1395/2017 አዳዲስ የገቢ ግብሮችንና የአከፋፈል ሁኔታዎችን ያካተተ ሲሆን ከዲጂታል ይዘት ፈጠራ የሚገኝ ገቢ ግብር የሚከፈልበት ስለመሆኑ ተደንግጓል።
አንቀጽ 53 "በኢትዮጵያ ዉስጥ የዲጂታል አገልግሎት በማቅረብ ገቢ የሚያገኝ ነዋሪ ወይም ነዋሪ ያልሆነ ማንኛዉም ሰዉ የሚያገኘዉ ገቢ ግብር ይከፈልበታል።" በሚል ተመልክቷል።
ይህም ገቢ ከዩትዩብ፣ከማህበራዊ ሚዲያ፣በኢንተርኔት ከሚሰራጭ መረጃ (ፖድካስቲንግ) በኢንተርኔት ከሚፈጸም ግብይት ከመሳሰሉት የሚገኝ ገቢ ነዉ።
ስለሆነም በኢትዮጵያ ዉስጥ የዲጂታል ይዘት አመንጪዎች የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር የማዉጣት፣ገቢን የማሳወቅ እና ሌሎች የታክስ ከፋይ ግዴታዎች ይኖሩባቸዋል፡፡

16/04/2025

በስህተት ወደ ባንክ አካዉንትታችን የገባን ገንዘብ ለባለገንዘቡ መመለስ የሞራል ግዴታ ብቻ ሳይሆነም የህግ ግዴታም ያለብን ስለመሆኑ፡-

የኛ ያልሆነ ገንዘብ በስህተት በባንክ አካዉንታችን ቢገባ በታማኝነት ለባለገንዘቡ መመለስ የሞራል ግዴታችን እንደመሆኑ የሚያስመሰግንንና የሚበረታታ ተግባር መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ በፍቃደኝነት ባንልመልስ ገንዘቡ የራስ የሚሆን ሳይሆን ባለገንዘቡ በህግ አግባብ ከሶ ገንዘቡን የምንመልስና ድርጊቱም የወንጀል ተጠያቂነት የሚያመጣ መሆኑን ልብ ሊባል ይገባዋል፡፡

15/04/2025

በፍትሐ ብሔር ስነስርዓት ሕግ ቁጥር 244 መሰረት በመጀመርያ ደረጃ መቃወሚያነት ሊነሱ ከሚችሉ መቃወሚያዎች በተጨማሪነት የሚከተሉት መቃወሚያዎች በመጀመርያ ደረጃ በክስ መቃወሚያነት ሊቀርቡ የሚችሉ ናቸዉ፡፡ ፡-
1. በአንድ ጉዳይ ተጠቃሎ መክስስ ሲገባ ነጣጥሎ ክስ ማቅረብ ። አንቀጽ 216
2. ከሳሽ መብት ወይም ጥቅም የለዉም በሚል የሚቀርብ መቃወሚያ። አንቀጽ 33(2)
3. ክሱ የቀረበበት ንብረት ግምት ላይ የሚቀርብ መቃወሚያ። አንቀጽ 250 ፡፡

08/03/2024

የስራ ስንብት ክፍያ እና ካሳ የሚከፈልባቸው ሁኔታች በአሰሪና ሰራተኛ ህግ

መግቢያ

የአሰሪና ሰራተኛ ህግ በአሰሪና ሰራተኛ መካከል ያለ ግንኙነት የሚያስተዳድር ህግ ሲሆን ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ የግል ሰራተኞች ከአሰሪዎቻቸው ጋር ያላቸውን ግንኘነት የሚገዙ የተለያዩ ህጎች በስራ ላይ እንደነበሩ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡ ከነዚህም ውስጥ በ1955 ዓ.ም የወጣው የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 210/1955፣ በ1968 ዓ.ም የወጣው የሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 64/1968፣ የሠራተኛ ጉዳይ ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 85/1968፣ ስለአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ የወጣው አዋጅ ቁጥር 42/1985 እና አዋጅ ቁጥር 377/1996 የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ በአሁኑ ወቅት ደግሞ ካለው የማህበረሰብ እድገት ጋር የሚጣጣም የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 ወጥቶ በስራ ላይ ይገኛል። በአዋጁ ከተካተቱ ጉዳዮች ውስጥ የስራ ውል የሚቋረጥባቸው ሁኔታዎች ይገኝበታል። ይኸውም የስራ ውል የሚቋረጠው በአሰሪው ወይም በሠራተኛው አነሳሽነት ወይም በህግ በተደነገገው መሰረት ወይም በኅብረት ስምምነት ወይም በተዋዋይ ወገኖች በሚደረግ ስምምነት እንደሚሆን በአዋጁ አንቀፅ 23/1 ስር ተደንግጎ ይገኛል። የስራ ውል ሲቋረጥ ያለማስጠንቀቂ (አንቀፅ 27) እና በማስጠንቀቂያ (አንቀጽ 28) ሊሆን እንደሚችል ከአዋጁ ድንጋጌዎች መገንዘብ ይቻላል። የስራ ውል መቋረጥ ከሚያስከትላቸው ውጤቶች መካከል ደግሞ የስራ ስንብት ክፍያ አንዱ ነው። የዚህ አጭር የንቃተ- ህግ ትምህርታዊ ፅሁፍ ትኩረት የስራ ውል ሲቋርጥ የስራ ስንብት እና የካሳ ክፍያ የሚከፈልባቸው ሁኔታዎች ምን ይመስላሉ የሚለው ይሆናል።

• የስራ ስንበት ክፍያ እና የካሳ ምንነት

የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ አዋጅ በተለምዶ የአገልግሎት ክፍያ እየተባለ ለሚታወቀው የስራ ስንብት ክፍያ ትርጉም ያልሰጠ ቢሆንም በተለያዩ ፅሁፎች ከተሰጠው ትርጉም መረዳት እንደሚቻለው የሥራ ስንብት ክፍያ ማለት አሠሪው ከቅጥሩ በኋላ ወይም ቅጥሩ ሲጠናቀቅ ለሠራተኛው የሚሰጠው ማካካሻ እና/ወይም ጥቅማጥቅሞች ነው። በአዋጁ ስለስራ ስንበት ክፍያ ከተቀመጡ አጠቃላይ ድንጋጌዎች የሚወሰደው ግንዛቤ ከዚህ ትርጉም ጋር የሚጣጣም ሆኖ ይገኛል። በተመሳሳይ አዋጁ ስለካሳ ምንነት ትርጉም ያልሰጠ ሲሆን ከድንጋጌዎቹ አጠቃላይ መንፈስ መረዳት እንደሚቻለው በአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ ካሳ ማለት በአሰሪው ጥፋት የስራ ውል ተቋርጦ ወደ ስራ እንዲመለስ ለሰራተኛ ፍርድ ቤት ወስኖለት ሰራተኛው ወደ ስራ ለመመለስ ፍቃደኛ ካልሆነ በስራ መቋረጥ ምክንያት አሰሪ ለሰራተኛው ገንዘብ በካሳ መልክ የሚከፍልበት የክፍያ አይነት ነው። አዋጁ ለስራ ስንብት ክፍያ እና ካሳ ትርጉም ያልሰጠ ቢሆንም ክፍያዎቹ የሚከፈሉበትን ሁኔታ እና የክፍያ ስሌቱን በዝርዝር አስቀመቀጧል።

• የስራ ስንበት ክፍያ የሚከፈልባቸው ሁኔታዎች

በአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 አንቀጽ 39 ስር የስራ ስንብት ክፍያ የሚከፈልባቸው ሁኔታዎች ተዘርዝረው ይገኛሉ። ይኸውም የሙከራ ጊዜውን የጨረሰ እና አግባብነት ባለው የጡረታ ህግ መሰረት የጡረታ አበል ለመቀበል ብቁ ያልሆነ ሰራተኛ በሚከተሉት ሁኔታዎች የስራ ስንብት ክፍያ ይከፈለዋል።

• ድርጅቱ በመክሰሩ ወይም በሌላ ምክንያት ለዘለቄታው በመዘጋቱ የሥራ ውሉ ሲቋረጥ ( በአዋጁ አንቀፅ 24/4 ተመልክቷል )፣
• በህግ ከተደነገገው ምክንያት ውጪ በአሰሪው አነሳሽነት የሥራ ውሉ ሲቋረጥ ( የስራ ውል በአሠሪ አነሳሽነት ሊቋረጥ የሚችልባቸው ህጋዊ አግባቦች በአዋጁ አንቀፅ 26 ተመልክተዋል)፣
• በአዋጁ በተመለከቱት ሁኔታዎች

20/05/2023
18/01/2023
21/12/2022

Address

Addis Ababa
ET2121

Telephone

251 927424162

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Konjit Legal Clinic posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category