01/05/2025
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኡጋንዳው ፕሬዝደንት ዩዌሪ ሙሴቪኒ ‹‹እኔ አፍሪካን በመከፋፈል አላምንም›› አሉ፡፡ ፕሬዝደንቱ የአለም የትምህርት ቀን ትላንት በተከበረበት ወቅት ባደረጉት ንግግር ‹‹እኔ አፍሪካን በመከፋፈል አላምንም፡፡ አሁን በአገራችን ውስጥ ኢትዮጵያዊያንን፣ ኤርትራዊያንን፣ ሱማሊያዊያንን፣ ደቡብ ሱዳናዊያንንና የሌሎችም አገራትን ዜጎች በብዛት ስመለከት ደስ ይለኛል፡፡ እነዚህ ዜጎች ህግን እስካልጣሱ ድረስ ኡጋንዳ አገራቸው ናት፡፡›› ብለዋል፡፡
ሙሴቪኒ ሲቀጥሉም ‹‹አፍሪካዊያን ከሳይንስና ቴክኖሎጂ ራሳቸውን ማራቅ የለባቸውም፡፡ ትምህርት ወሳኝ ነገር ቢሆንም ለሳይንስና ቴክኖሎጂ ትልቅ ትኩረት ይገባል፡፡›› በማለት ገልፀዋል፡፡
ፕሬዝደንቱ አለም አቀፍ የትምህርት ቀንን አስመልክቶ በተደረገው ዝግጅት ላይ ይህንን ንግግር ካደረጉ በኋላ ከኢትዮጵያዊያን የሀይማኖት አባቶች ጋር ፎቶ መነሳታቸውን ኔክሰስ ሚዲያ ካቀረበው ዘገባ ተመልክተናል፡፡