ጠበቃ ተወልደብርሃን ዕፃይ ፀጋዝኣብ

ጠበቃ ተወልደብርሃን ዕፃይ ፀጋዝኣብ prevailing justice

  ከተከራካሪ ወገኖች ውጭ በሥነ-ሥረዓት ህጉ መሠረት ወደ ክርክሩ እንዲገባ ሳያደርጉ ለ3ተኛ ወገን ንብረት ነው በማለት የሚሰጡት ውሳኔ መሠረታዊ የህግ ስህተት የተፈፀመበት መሆኑን   በመዝገ...
29/08/2026

ከተከራካሪ ወገኖች ውጭ በሥነ-ሥረዓት ህጉ መሠረት ወደ ክርክሩ እንዲገባ ሳያደርጉ ለ3ተኛ ወገን ንብረት ነው በማለት የሚሰጡት ውሳኔ መሠረታዊ የህግ ስህተት የተፈፀመበት መሆኑን በመዝገብ ቁጥር 162628 በሆነው የሰጠው ውሳኔ።

ፍርድ ቤቶች ከተካራካሪ ወገኖች መካከል ጣልቃ ገብ ተከራካሪው በሥነ ሥርዓት ሕጉ መሰረት ወደ ክርክሩ እንዲገባ እና ክርክሩን እንዲያቀርብ ባልተደረገበት ሁኔታ፣ ዳኝነት ባልተከፈለበት፣ለክርክር ምክንያት የሆነዉ ንብረት የዉርስ ሀብት ሳይሆን የ3ኛ ወገን ንብረት ነዉ በማለት መወሰን የማይቻል ስለመሆኑ፡፡
የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ.182 (2)፤40 (2)

ከይዞታዬ ላይ ተቀንሶ ያለአግባብ ለሌላ የተሰጠው ካርታ እንዲመክን በሚል የሚቀርብ ክስ በቀጥታ ለፍርድ ቤት የሚቀርብ ሳይሆን በአስተዳደር ስነ ስርዓት አዋጅ 1183/2012 አንቀጽ 44 መሰረ...
25/08/2026

ከይዞታዬ ላይ ተቀንሶ ያለአግባብ ለሌላ የተሰጠው ካርታ እንዲመክን በሚል የሚቀርብ ክስ በቀጥታ ለፍርድ ቤት የሚቀርብ ሳይሆን በአስተዳደር ስነ ስርዓት አዋጅ 1183/2012 አንቀጽ 44 መሰረት ለተቋቋመ የአስተዳደር ተቋም የቅሬታ ማስተናገጃ አካል በአንቀጽ 43 ቅሬታ የሚቀርብበትና ይህ ቅሬታ ሰሚ አካል በአንቀጽ 46 መሰረት የተቋሙን መጨረሻ ዉሳኔ ሲሰጥ በአንቀጽ 49(1) አግባብ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የክለሳ አቤቱታ የሚቀርብበት ነዉ፡፡

ይህን ወደ ጎን በማለት ከሳሽ በአዋጁ በተዘረጋዉ ስርዓት መሰረት ያሉትን ሂደቶች ተከትሎ ያንን ከጨረሱ (exhaustion of available remedies) በኋላ መምጣት ሲገባቸዉ ቀጥታ ለፍርድ ቤት ያቀረቡት ክስ አዋጁን ያገናዘበ አይደለም።

ስለሆነም የካርታ ይምከንልኝ ክስ በአስተዳደር ስነ ስርዓት አዋጅ 1183/2012 አንቀጽ 43 እና 44 የተዘረጋውን ስነ ስርዓት ሳይጠብቅ የቀረበ ከሆነ ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን የማየት ስልጣን የለውም።

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰበር መዝገብ ቁጥር 220042 ሕዳር 30 ቀን 2015 ዓ.ም የሰጠው ውሳኔ

Via:Jura Legal Update

information,መረጃ/ሓበሬታዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ)  ላይ ፍ/ቤቶች ያላቼው ስልጣን በኢትዮጵያ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) ላይ በስሕተት የተመዘገበ መረጃ ካለ ተቋሙ አጣርቶ በራሱ የማስ...
21/08/2026

information,መረጃ/ሓበሬታ
ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) ላይ ፍ/ቤቶች ያላቼው ስልጣን

በኢትዮጵያ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) ላይ በስሕተት የተመዘገበ መረጃ ካለ ተቋሙ አጣርቶ በራሱ የማስተካከል ሥልጣን አለው::
ስለሆነም ፍርድ ቤቶች “በፋይዳ መታወቂያ ላይ የተፈጠረ ስሕተት ይታረምልኝ” የሚሉ አቤቱታዎችን በቀጥታ ተቀብለው የማየት ሥልጣን የላቸውም::
ፍ/ቤቶች የዚህ ዓይነት አቤቱታዎችን መቀበል የሚችሉት ተቋሙን አስተዳደራዊ መፍትሔ ጠይቀው ካልተሰጣቸው ወይም የተሰጣቸው መፍትሔ ላይ ቅሬታ ካላቸው ብቻ ነው::
" የኢትዮጵያ ብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም
ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም

የማስረጃ ምዘና መርኅን ስለመጣስ:- ፍርድ ቤቶች የቀረቡላቸውን ማስረጃዎች በሙሉ (የሰው ምስክርም ሆነ የሰነድ) መርምረውና መዝነው ፍሬ ነገርን የማጣራት ኃላፊነት አለባቸው:: (ሰ/መ/ቁ. 2...
20/08/2026

የማስረጃ ምዘና መርኅን ስለመጣስ:-
ፍርድ ቤቶች የቀረቡላቸውን ማስረጃዎች በሙሉ (የሰው ምስክርም ሆነ የሰነድ) መርምረውና መዝነው ፍሬ ነገርን የማጣራት ኃላፊነት አለባቸው:: (ሰ/መ/ቁ. 208495)
በተለይም፣ የቀረበን የሠነድ ማስረጃ ከግምት ውስጥ ሳያስገቡ ወይም ሳይመረምሩ በሰው ምስክሮች ቃል ላይ ብቻ ተመሥርቶ የሚሰጥ ውሳኔ የማስረጃ ምዘና መርኅን የሚጥስና መሠረታዊ የህግ ስህተት ያለበት ነው:: (ሰ/መ/ቁ. 208495 -30/5/2013 ዓ.ም
followers

🚨 የፌዴሬሽን ምክር ቤት ታሪካዊና አስደናቂ ውሳኔ ሰጠ!በግንባታ ውል አፈጻጸም ላይ የተነሳውን ግዙፍ የገንዘብ ክርክር አስመልክቶ የቀረበውን የሕገ መንግሥት ትርጉም ጥያቄ መሠረት በማድረግ፣ ...
20/08/2026

🚨 የፌዴሬሽን ምክር ቤት ታሪካዊና አስደናቂ ውሳኔ ሰጠ!
በግንባታ ውል አፈጻጸም ላይ የተነሳውን ግዙፍ የገንዘብ ክርክር አስመልክቶ የቀረበውን የሕገ መንግሥት ትርጉም ጥያቄ መሠረት በማድረግ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ፍርድ ቤቶች የሰጡትን ውሳኔ ሽሮ በሙሉ ድምፅ ወሳኝ ትዕዛዝ አስተላልፏል!
📌 የጉዳዩ ዋና ዋና ነጥቦች፦
* ግዙፍ የገንዘብ ክርክር፦ በአመልካች (ግንቦ ገበያ ንግድ አክሲዮን ማህበር) እና በተጠሪ (አቶ ጄነራል ገራሱ ሀበበ) መካከል ከተፈጸሙ የሕንፃ ግንባታ ውሎችና ተጨማሪ ሥራዎች ጋር በተያያዘ ከ 150 ሚሊዮን ብር በላይ ክፍያን የሚመለከት አለመግባባት ተፈጥሮ ነበር।
* የግልግል ዳኝነት (Arbitration) ስምምነት፦ ሁለቱም ወገኖች በውላቸው ላይ አለመግባባቶች ሲፈጠሩ ጉዳዩ በግልግል ዳኝነት እንዲታይ የተስማሙ ቢሆንም፣ መደበኛ ፍርድ ቤቶች ግን ውሉን ችላ በማለት ጉዳዩን ተቀብለው ውሳኔ ሰጥተውበት ነበር।
* የሕገ መንግሥት ጥሰት፦ የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ ጉዳዩን መርምሮ፣ ወገኖች አለመግባባታቸውን በግልግል ዳኝነት ለመጨረስ ያደረጉት ስምምነት በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 37(1) የተረጋገጠውን ፍትሕ የማግኘት መብት አካል መሆኑን አረጋግጧል።
* ፍርድ ቤቶች የሰጡት ውሳኔ ተሻረ፦ ውሉን በመጣስና የሕገ መንግሥቱን መሠረታዊ መርሆዎች በመጣስ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ቻሎት ሳይቀር ጸንቶ የነበረው ውሳኔ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 9(1) መሠረት ተሻሯል (ሕጋዊ ተፈጻሚነት የለውም) ተብሏል።
⚖️ የተሰጠው የመጨረሻ ውሳኔና ትዕዛዝ፦
* ጉዳዩ በወገኖች መካከል በተደረገው ውል መሠረት በግልግል ዳኝነት (Arbitration) መታየት አለበት።
* የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ቻሎት የሰጠው ውሳኔ እንዲሻር ተደርጓል።
* የፌዴሬሽን ምክር ቤት የሕገ መንግሥት አጣሪ ጉባኤ ያቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ በሙሉ ድምፅ አጽድቆታል።
Via habtamu tibebu

  ስብራት ጉዳት በወንጀል ህግ አንቀጽ 556(2) ወይስ በአንቀጽ 555 መሠረት ሊያስጠይቅ የሚችለው?  ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 219862 በሆነው በቅጽ 28 ላይ የተሰጠ...
19/08/2026

ስብራት ጉዳት በወንጀል ህግ አንቀጽ 556(2) ወይስ በአንቀጽ 555 መሠረት ሊያስጠይቅ የሚችለው?

ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 219862 በሆነው በቅጽ 28 ላይ የተሰጠ አስገዳጅ የሰበር ውሳኔ።

በፈፀመው የወንጀል ድርጊት የተጎጂው አጥንት መሰበሩ የተረጋገጠ ቢሆንም ስብራቱ ታክሞ መዳኑ በባለሙያ ከተረጋገጠና በስብራቱ ምክንያት የተጎጂ ሰውነትም ሆነ በአይምሮው ላይ ለዘወትር
ጠንቅ የሚያተርፍ መሆኑ ፤ከአካሉ ወይም አስፈላጊ ከሆኑ ብልቶች መካከል አንደ ወይም ከዘያ በላይ መጉደለ እና በጉዳቱ ምክንያት አስፈላጊው ብልት አገልግሎት አለመስጠቱ ወይም በሚያሳቅቅ ጉልህ
ሆኖ በሚታይ ሁኔታ የተጎጂው መልክ መበላሸቱ፤ ወይም በማናቸውም ሌላ መንገድ ሌላ ከባድ የሆነ ጉዳትን ወይም በሽታን
የሚያስከትል መሆኑ ካልተረጋገጠ በስተቀር ተጎጂ ላይ የደረሰው አጥንት ስብራት ታክሞ መዳኑ ከተረጋጠ ድርጊቱ የሚሸፈነው
በወንጀል ሕግ አንቀፅ 556(2) በመሆኑ ቅጣቱ ሊጣልበት የሚገባው በወንጀል ህግ አንቀጽ 556(2)መሠረት ስለመሆኑ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 219862 በሆነው በቅጽ 28 ላይ የተሰጠ ውሳኔ።

ደመላሽ ንጋቱ

ካርታ ይሰረዝልኝ እንዲሁም ንብረት የጋራ መሆኑ በፍርድ እንዲረጋገጥልኝ በሚል የቀረበ የዳኝነት ጥያቄ ከአስተዳደር ስነ-ስርዓት አዋጅ ቁጥር 1183/2012 አንቀጽ 44 እና 49 ከደነገጉት እ...
19/08/2026

ካርታ ይሰረዝልኝ እንዲሁም ንብረት የጋራ መሆኑ በፍርድ እንዲረጋገጥልኝ በሚል የቀረበ የዳኝነት ጥያቄ ከአስተዳደር ስነ-ስርዓት አዋጅ ቁጥር 1183/2012 አንቀጽ 44 እና 49 ከደነገጉት እንዲሁም የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመ.ቁ 220042 እና በመ.ቁ 220582 ከሰጠው የህግ ትርጉም አንጻር ሲታይ ከካርታ ይሰረዝልኝ በተጨማሪ የንብረት ባለቤትነት በፍ/ቤት ውሳኔ እንዲረጋገጥ ዳኝነት የተጠየቀበት በመሆኑ ጉዳዩን የማየት የዳኝነት ስልጣን ያለው [የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የአስተዳደር ችሎት ሳይሆን] የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ነው።

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰበር መዝገብ ቁጥር 235053 መጋቢት 29 ቀን 2015 ዓ.ም የሰጠው ውሳኔ

via Jura Legal Update

🚨 ሰበር ዜና፦ ከቤት ንብረት እና የህግ ክርክር ጋር የተያያዘ ታላቅ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ! ⚖️📜የፌዴሬሽን ምክር ቤት የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሰጠውን ውሳኔ በ...
11/08/2026

🚨 ሰበር ዜና፦ ከቤት ንብረት እና የህግ ክርክር ጋር የተያያዘ ታላቅ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ! ⚖️📜
የፌዴሬሽን ምክር ቤት የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሰጠውን ውሳኔ በሙሉ ድምፅ ሽሮታል!
🔍 የክርክሩ አመጣጥና የጉዳዩ መነሻ (Case Summary)
* የቦታውና የቤቱ መነሻ፦ ጉዳዩ በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 (ቀደም ሲል ወረዳ 10 ቀበሌ 15) የሚገኘውን የቤት ቁጥር 094 እና 095 ይዞታን የሚመለከት ነው።
* የባለቤትነት ክርክሩ፦ ግለሰቦቹ (ተጠሪዎች) ቤቱ በአዋጅ ቁጥር 47/67 መሠረት ያልተወረሰና የሟች ወላጆቻቸው የግል ንብረት መሆኑን በመጥቀስ እንዲመለስላቸው ሲከራከሩ ቆይተዋል።
* የሥር ፍርድ ቤቶች ውሳኔ፦ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 200305 አከራካሪው ቤት ለተጠሪዎች (ለግለሰቦቹ) እንዲረከቡ ውሳኔ ሰጥቶ ነበር።
* የመንግሥትና የምክር ቤቱ ሞገት፦ ቤቱ ለረጅም ዓመታት በመንግሥት እጅ የቆየ፣ ሲያከራየውና ሲያስተዳድረው የነበረ በመሆኑ “በመንግሥት እጅ ለረጅም ጊዜ የቆዩ ቤቶች የመንግሥት ናቸው” የሚለውን መመሪያ መሠረት በማድረግ ጉዳዩ እስከ ሕገ-መንግሥት ትርጉም አባሪ ጉባኤና ፌዴሬሽን ምክር ቤት ደርሷል።
🏛️ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የወሰነው ዋና ዋና ነጥቦች
* 🛑 የሰበር ውሳኔ መሻር፦ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሰጠው ውሳኔ ከሕገ-መንግሥቱ ጋር የሚቃረን በመሆኑ በሙሉ ድምፅ ተሽሯል።
* 🏠 የቤት ይዞታው የመንግሥት ነው፦ ለረጅም ጊዜ በመንግሥት ቁጥጥር ስር የነበሩና ሲስተዳደሩ የቆዩ ቤቶች የመንግሥት እንደሆኑ የሚቆጠሩ በመሆኑ፣ አከራካሪው ቤት የመንግሥት ይዞታ መሆኑ ጸንቷል።
* ⚖️ ሕገ-መንግሥታዊ የበላይነት፦ የሰበር ሰሚ ችሎቱ ውሳኔ በሕገ-መንግሥቱ አንቀጽ 9(1) እና 37(1) መሠረት ተፈጻሚነት እንዳይኖረው ተደርጓል።
> 💡 ለሕግ ባለሙያዎች፣ ለይዞታ ባለቤቶችና ፍትህ ተከታታዮች በጣም አስፈላጊ መረጃ ነው!
> መረጃው ለሌሎችም እንዲደርስ አሁኑኑ LIKE & SHARE በማድረግ ያጋሩ! 👇
Via habtamu tebebu

®በዳኞች አስተዳደር አብይ ጉባዔ የሚወሰን የዳኞች የስንብት ዉሳኔ ምክር ቤት ቀርቦ ከመፅደቁ በፊት ፍርድ ቤት ቀርቦ የመታየቱ ጉዳይንም ይህ የህገ መንግስት ትርጉም ያካትተው ይሆን?® የዳኞች...
07/08/2026

®በዳኞች አስተዳደር አብይ ጉባዔ የሚወሰን የዳኞች የስንብት ዉሳኔ ምክር ቤት ቀርቦ ከመፅደቁ በፊት ፍርድ ቤት ቀርቦ የመታየቱ ጉዳይንም ይህ የህገ መንግስት ትርጉም ያካትተው ይሆን?

® የዳኞች የስንብት ውሳኔ ምክር ቤት ከመቅረቡ በፊት በይግባኝም ሆነ በሰበር ቀርቦ እንዳይመዘን የተደረገበት አመክንዬ ምንድን ነው?
~~~
የፌዴሬሽን ምክር ቤት 6ኛ የፓርላማ ዘመን፣ 5ኛ ዓመት የሥራ ጊዜ፣ 1ኛ መደበኛ ጉባዔ መስከረም 27 ቀን 2018 ዓ.ም መ/ቁ 142/17 በሰጠው ውሳኔ፣ ማንኛውም የመንግስት አካል የሚያወጣቸው ሕጎች የትኛውም መስሪያ ቤት ወይም የስራ ሃላፊ በሠራተኞች ላይ የሚሰጠው የስንብት ውሳኔ በፍርድ ቤት ወይም በዳኝነት አካላት ዘንድ ቀርበው እንዳይታዩና ውሳኔ እንዳያገኙ መከልከል ከሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 37(1) ጋር የሚቃረኑ በመሆናቸው ተፈጻሚነት እንዳይኖራቸው የሕገ መንግስት ትርጉም ውሳኔ አስተላልፏል፡፡
Via voice justice

በአዋጅ ቁጥር 322/1995 መሰረት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በተደራጀባቸው ክልሎች ያሉ የክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች በኢፌዲሪ ሕገ መንግስት አንቀጽ 78(2) እና 80(4) ድንጋጌ  በተሰ...
07/08/2026

በአዋጅ ቁጥር 322/1995 መሰረት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በተደራጀባቸው ክልሎች ያሉ የክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች በኢፌዲሪ ሕገ መንግስት አንቀጽ 78(2) እና 80(4) ድንጋጌ በተሰጣቸዉ የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የዉክልና ስልጣናቸዉ በቀጥታ ያዩዋቸዉን የፈዴራል ጉዳዮች በይግባኝ የማየት ስልጣን ያላቸዉ የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች ሳይሆኑ በክልሉ እንዲደራጁ የተደረጉት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች ናቸው ተብሎ ተወስኗል፡፡

Address

Mek'ele

Telephone

+251914555690

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ጠበቃ ተወልደብርሃን ዕፃይ ፀጋዝኣብ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share