Triangle Law Firm LLP

Triangle Law Firm LLP በትጋት! በብቃት ! በእምነት! እናገለግላለን::

12/08/2026

ለአማራ ክልል ጠበቆች መልካም ዜና
^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^

የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ የጠበቆችን የገቢ ግብር አከፋፈል በተመለከተ እንዲሁም ከVAT ምዝገባ ጋር በተገናኘ ላለው ውዝግብ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድቤት የሰጠውን እግድ መሰረት በማድረግ ለሁሉም ጠበቆች ወጥ የሆነ አሰራር እንድተገበር የሚያስችል ግልፅ ማብራሪያ ሰጥቷል።

ዝርዝር ጉዳዮችን በዚህ ሊንክ ከሚገኘው https://t.me/Lisanehig channel የክልሉ ገቢዎች ቢሮ የላከውን ደብዳቤ ይመልከቱ!!


ለአማራ ክልል ጠበቆች ማህበር እና ለአመራሮቹ!!

10/08/2026

የስልጣን ክፍፍልን (Horizontal Separation of Power) የተመለከተ በፌዴሬሽን ምክርቤት የተሰጠ የሕገ-መንግስት ትርጉም ነው።

የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ሠራተኛ የሥራ ማዕረግ የሚወሰነው ሕግ አውጪው በሚያወጣው ሕግ ብቻ ነው። በመሆኑም ፍርድ ቤቶች ከሕግና ከአስፈጻሚው ውሳኔ ውጭ የራሳቸውን ትርጉም በመስጠት ያልተፈቀደ ጥቅማ ጥቅም እንዲከፈል መወሰናቸው የሥልጣን ክፍፍል መርህን የሚጥስ ነው።

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት፣ መስከረም 27 ቀን 2018 ዓ.ም በመዝገብ ቁጥር 137/17 የተሰጠ ውሳኔ ነው።

ሙሉ መረጃውን (ዝርዝር ውሳኔውን) ከታች ካለው የቴሌግራም ቻናል ማግኘት ይችላሉ።
https://t.me/Lisanehig

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድቤት የፍርድቤቶችን የክረምት ስራ ሁኔታ በተመለከተ የሰጠው አጭር ጋዜጣዊ መግለጫ!!
06/08/2026

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድቤት የፍርድቤቶችን የክረምት ስራ ሁኔታ በተመለከተ የሰጠው አጭር ጋዜጣዊ መግለጫ!!

ፌዴራል ጠቅላይ ሸሪዓ ፍርድ ቤት አዲስ ተሿሚ አመራሮች የሥራ ርክክብ አደረጉ©©©©©©©ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም (የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት)የፌዴራል ጠቅላይ ሸሪዓ ፍርድ ቤት አዲስ የተሾሙ...
06/08/2026

ፌዴራል ጠቅላይ ሸሪዓ ፍርድ ቤት አዲስ ተሿሚ አመራሮች የሥራ ርክክብ አደረጉ
©©©©©©©

ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም (የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት)

የፌዴራል ጠቅላይ ሸሪዓ ፍርድ ቤት አዲስ የተሾሙ አመራሮች በዛሬው ዕለት የሥራ ርክክብ አድርገዋል፡፡

‎የፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ሐምሌ 22 ቀን 2018 ዓ/ም ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ በፈቃዳቸው መልቀቂያ ባስገቡት የፌዴራል ጠቅላይ ሸሪዓ ፍርድ ቤት አመራሮች ምትክ በኢትዮጵያ እስልምና ጠቅላይ ምክር ቤት ተመልምለው የቀረቡ እጩዎችን ተገቢውን ማጣራት በማድረግ ሹመት መስጠቱ ይታወሳል።

‎ክቡር ሼህ መከተ ሙሄ መኮንን የፌዴራል ጠቅላይ ሼሪ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት እንዲሁም ክቡር ሼህ አብዱልመናን መሐመድ አህመዲን የፌዴራል ጠቅላይ ሼሪዓ ፍርድ ቤት ም/ፕሬዝዳንት ሆነው እንዲሰሩ በተሾሙት መሰረት በዛሬው ዕለት ከቀድሞ የፍርድ ቤቱ ፕሬዝዳንት ክቡር ሼህ ሙባራክ ሼህ መሐመድ አወል እና ምክትል ፕሬዝዳንት ክቡር ሼህ ሸረፈዲን ሚስባህ የስራ ርክክብ አድርገዋል።

‎የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት በስራ ርክክቡ ወቅት፤ የፌዴራል ሼሪዓ ፍርድ ቤቱን እስከ ዛሬ ድረስ በፕሬዝዳንትነት እና በምክትል ፕሬዝዳንትነት ሲያገለግሉ የነበሩ አመራሮችን ላበረከቱት አስተዋጽኦ አመስግነው፤ በዛሬው ዕለት ኃላፊነት ለተረከቡት አዲስ አመራሮች የበለጠ መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚገባቸው በማሳሰብ መልካም የስራ ዘመን እንዲሆንላቸው ምኞታቸውን ገልጸዋል።

‎የስራ ርክክቡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረትን ጨምሮ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ተከናውኗል።

መረጃው የፌደራል ጠቅላይ ፍርድቤት ነው።

ማንኛውም የመንግስት አካል የሚያወጣቸው ሕጎች የትኛውም መስሪያ ቤት ወይም የስራ ሃላፊ በሠራተኞች ላይ የሚሰጠው የስንብት ውሳኔ በፍርድ ቤት ወይም በዳኝነት አካላት ዘንድ ቀርበው እንዳይታዩና...
06/08/2026

ማንኛውም የመንግስት አካል የሚያወጣቸው ሕጎች የትኛውም መስሪያ ቤት ወይም የስራ ሃላፊ በሠራተኞች ላይ የሚሰጠው የስንብት ውሳኔ በፍርድ ቤት ወይም በዳኝነት አካላት ዘንድ ቀርበው እንዳይታዩና ውሳኔ እንዳያገኙ መከልከል ከሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 37(1) ጋር የሚቃረኑ በመሆናቸው ተፈጻሚነት እንዳይኖራቸው የሕገ መንግስት ትርጉም ውሳኔ አስተላልፏል፡፡

የፌዴሬሽን ምክር ቤት 6ኛ የፓርላማ ዘመን፣ 5ኛ ዓመት የሥራ ጊዜ፣ 1ኛ መደበኛ ጉባዔ መስከረም 27 ቀን 2018 ዓ.ም መ/ቁ 142/17 በሰጠው ውሳኔ።

06/08/2026
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም በ6ኛው የፓርላማ ዘመን 5ኛ ዓመት 2ኛ መደበኛ ጉባኤ በመዝገብ ቁጥር 150 በመንግሥት አካል ሕጋዊ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ የ...
04/08/2026

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም በ6ኛው የፓርላማ ዘመን 5ኛ ዓመት 2ኛ መደበኛ ጉባኤ በመዝገብ ቁጥር 150 በመንግሥት አካል ሕጋዊ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ የተሰጠው ሰው፣ የመሬቱ ሕጋዊ ባለይዞታ የመሆን እና በመሬቱ የመጠቀም ሕገ መንግሥታዊ መብቱ የተጠበቀ ነው።
​አንድ ሰው የሌላ ሕጋዊ ባለይዞታ በሆነ መሬት ላይ (ባለይዞታው ሳይቃወመው እንኳን ቢሆን) ቤት ቢሠራ፣ የመሬቱ ባለይዞታነት ወይም የቤቱ ሙሉ ባለሃብትነት ወደ ቤቱ ሠሪ አይተላለፍም።

​የሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 40(7) "በመሬት ላይ ንብረት ያፈራ ሰው የንብረቱ ባለቤት ይሆናል" የሚለው ድንጋጌ የሚሠራው የመሬት ባለይዞታነት መብት ላለው ሰው እንጂ፣ በሌላ ሰው ይዞታ ላይ ያለ ሕጋዊ መሠረት ንብረት ለገነባ ሰው የቤት ባለቤትነት መብት ለመስጠት አይደለም።

​ባለይዞታው ሳይቃወም በይዞታው ላይ ቤት የሠራ ሰው የሚኖረው ሕገ መንግሥታዊ መብት ለቤቱ/ለግንባታው ያወጣውን ወጪ (ግምት) ከመሬቱ ባለይዞታ የመጠየቅ መብት ብቻ ነው።
​በመሆኑም የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት "በሌላ ሰው መሬት ላይ ቤት የሠራ ሰው የቤቱ ባለቤት ይሆናል" በማለት የሰጣቸውን የቀደሙ አስገዳጅ ውሳኔዎች ኢ-ሕገ መንግሥታዊ ናቸው በማለት የሕገ መንግስት ትርጉም ውሳኔ ሰጥቷል።

"Presumption of Innocent"  vs "Beyond a reasonable doubt" Standard of proof in Criminal Prosecution.  ------------------...
03/08/2026

"Presumption of Innocent" vs "Beyond a reasonable doubt" Standard of proof in Criminal Prosecution.
---------------------
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም በ6ኛው የፓርላማ ዘመን 5ኛ ዓመት 2ኛ መደበኛ ጉባኤ በመዝገብ ቁጥር 151 በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 20(3) መሠረት ነፃ ሆኖ የመገመት መብት በዓቃቤ ሕግ ላይ የሚጥለው አነስተኛ የማስረዳት ደረጃ ወንጀሉ በተከሳሹ ስለመፈጸሙ ከምክንያታዊ ጥርጣሬ በጸዳ ሁኔታ (Beyound Resonable Doubt) የማስረዳት ሸክም ነው በማለት አስገዳጅ የሕገ መንግስት ትርጉም ውሳኔ ተሰጥቷል።

Address

Addis Abeba
Dessie

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Triangle Law Firm LLP posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share