01/06/2026
ባህር ዳር ከተማ ቀበሌ 14 አዲሱ እስታዲዮም አጥር ጥግ ያለን እግረኛ መንገድ በሚታይ መልኩ የመንገድ መሀል አትክልት ላይ ያለን አፈር ቀንሰው መንገድ ላይ ከምረው ነበር ያንን አፈር በመኪና ሲያነሱ ነበር እዚህ አካባቢ ግን ሎደሩ አንስቶ አትክልት ወደ ሚያፈሉት ዳር ሲያወጣ በሚታየው መልኩ እግረኛ መንገዱን በዚህ መልኩ አፈራርሶታል ንዶታል።
በእግረኛ መንገድ ላይ መኪና አሽከረከርክ በሚል ብዙ መቶሽህ ብሮች ቅጣት ሲቀጡ ባየንበት ሀገራችን ውስጥ የመንግስት ሎደር በዚህ መልኩ በከተማው መሰረተ ልማት ላይ ውድመት ሲፈጥር ማነው የሚጠየቅ ??
ሌላ ሾፌር ይህንን ቢያደርግ ቀጣነው ያዝነው እየተባለ በሚዲያ መለፈፉ አይቀርም ነበር በራሳቸው በእነሱ ሲወድም ግን ተጠያቂም ጠያቂም የለም።
ባህር ዳር ከተማ አስተዳደር በሚሰሩ የመሰረተ ልማት ዝርጋታወች የኮሪደር ልማቶች በሚገነቡ ሰአት ለሌሎች መሰረተ ልማቶች ጥንቃቄን ማድረግ ላይ ክፍተት አለ አስፖልት ላይ አፈር ይከምራሉ በሎደር አስባልቶን እየፋቀ ያነሳሉ ስሚንቶ ያቦኩበታል ብዙ ብዙ ግድፈት አለ።
ከተማ አስተዳደሩ አንዱን ሲሰሩ አይዱን እያወደሙ በምስሉ እንደሚታየው ከጥቅም ውጭ እያደረጉ ያሉትን ሊያርም ልኮረኩም ሊያስተምር ይገባዋል ሲሉ መልዕክት አድርሰውናል።
Goshu Endalamaw Wondimagegn
Arega Kebede Legas/አረጋ ከበደ ለጋስ