16/05/2026
ሀገር ማለት … ?
ሀገራት ስለሀገር ትርጉም እና ምንነት ለመግለጽ እስከ አሁን ከሞንቴ ቪዲዮ ኮንቬንሽን (Monte Video Convention On the Right and duties of States: 26 December 1933) የተሻለ ሰነድ አለ ለማለት እቸገራለሁ
በዚህ በሞንቴቪዶ የቃል ኪዳን ሰነድ ውስጥ ሀገር እንደ አንድ አለም አቀፍ የሕግ ሰውነት እንዳለው አካል አረት መሠረታዊ ጉዳዮችን መያዝ እንዳለባት ተደንግጎ ይገኛል፡፡ በቃል ኪዳኑ አንቀጽ አንድ መሠረት ሀገር በአለም አቀፍ ህግ የህግ ሰውነት የሚኖረው ቋሚ ህዝብ፤የተወሰነ ድንበር ወይም ወሰን፤መንግስት እና ከሌሎች ሀገራት ጋር ህጋዊ ስራዎችን ለመስራት ብቁ ሲሆን ነው ይላል፡፡
ሀገር ማለት ከላይ እንደ ተገለፀው ህዝብ፤ ድንበር/ግዛት፤ መንግስት እና ከሌሎች ሀገራት ጋር የመስራት ህጋዊ ብቃት ከሆነ እውቅና (Recognition) ለምን አስፈለገ? ይኸው በመግቢያው የተገለፀው የሞንቴቪዶ ቃልኪዳን ሰነድ ሀገር ያለ እውቅና መቆም ትችላለች ይለናል በአንቀጽ ሦሥት ስር፡፡
“The political existence of the state is independent of recognition by the other states. Even before recognition the state has the right to defend its integrity and independence, to provide for its conservation and prosperity, and consequently to organize itself as it sees fit, to legislate upon its interests, administer its services, and to define the jurisdiction and competence of its courts.”
የአንድ ሀገር ህልውና በሌላ ሀገር እውቅና ላይ የተመሠረተ አይደለም፡፡ ከእውቅናም በፊት አንድ ሀገር ሉዓላዊነቱን እና ነፃነቱን የማስከበር፤ለብልጽግና እና እድገቱ መጠበቅ፤እና በዚህም መሠረት ይሆናል ባለው መልክ እራሱን የማደራጀት፤ጥቅሞቹን በህግ መደንገግ እና አግልግሎቶቹን ማስተዳደር እና የፍርድ ቤቶቹን ፍቅደ ስልጣንና ብቃት መደንገግ ይችላል ወይም የመወሰን መብት አለው፡፡
የሶማሊላንድ ሀገርነት እና የሰሞኑ የእስራኤል የሀገርነት እውቅና
ይህ ከሆነ ታዲያ ለአንድ ሀገር እንደ ሀገር መቆጠር እውቅና ለምን አስፈለገ? ሶማሊላንድ ሀገር አይደለችም? የሀገርነት እውቅና ለምን አስፈለጋት?
ሶማሊላንድ በእንግሊዝ ቅኝ ግዛት ስር የነበረች እና ነፃነቷን እንደ ማንኛውም የአፍሪካ ሀገሮች ከተጎናፀፈች በኃላ በጣሊያን ሶማሊላንድ ወይም ከዛሬዋ ሶማሊያ ጋር በSomali Youth League እንቅስቃሴ ስር ታላቋን ሶማሌ ለመመስረት መቀላቀሏን ከተፃፉ ታሪኮች መረዳት ይቻላል፡፡ እውቁ የኢትኖግራፊ ፀሐፊ አፈንዲ ሙተቂ እንዲህ በማለት በማህበራዊ ሚዲያ ገፁ ለጥፎ አግኝቻለሁ፡፡
“ እንግሊዝ በ1880 ገደማ የአሁኑን የሶማሊላንድ ግዛት በወረራ ያዘችውና "British Somaliland" አለችው። ኢጣሊያ ደግሞ በ1890 ገደማ ከቦሳሶ እስከ ኪስማዮ ያለውን መሬት ያዘችና "Italian Somaliland" አለችው። በእነዚህ ግዛቶች ዘመናዊ ቅርጽ ያላቸውና የተደራጁ የቅኝ ግዛት መንግሥታት ተፈጠሩ።
ሁለቱ ግዛቶች በዚህ ሁኔታ ከሰባ ዓመታት በላይ ካሰለፉ በኋላ በ1961 ነፃነታቸውን ተቀዳጁ። ለሁለቱ ግዛቶች ነፃ መውጣት ትልቅ ትግል ያደረገው "Somali Youth League" የሚባል ድርጅት ነው።
ይህ ሊግ በሁለቱም ግዛቶች ቅርንጫፎች ነበሩት። ከዓላማዎቹ አንዱ የተበታተኑትን የሶማሊያ ግዛቶች አንድ ላይ ማሰባሰብ የሚል ነው። በመሆኑም ግዛቶቹ ነፃነታቸውን በሚያገኙበት ዋዜማ ላይ "አንድ መሆን አለብን" የሚል ጥያቄውን አጦዘው።
ሶማሊላንድ June 26/1960 ነፃነቷን ተቀዳጀች። ይህ ነፃነቷ ለአምስት ቀናት ብቻ ቢቆይም 35 ሀገራት (ግብጽ፣ ሊቢያ እና ኢትዮጵያን ጨምሮ) እውቅና ሰጥተዋል። የኢጣሊያ ሶማሊላንድ ደግሞ ከአምስት ቀን በኋላ (July 1/1960) ነፃ ወጣች። በስድስተኛው ቀን በሁለቱ ሀገራት ጠንካራ መሠረት የነበረው Somali Youth League የሰሜኑን ክፍል (ሶማሊላንድ) ተወካዮቹን በጥድፊያ ወደ ሞቃዲሾ አምጥቶ ሶማሊያ አንድ ሀገር መሆኗን አወጀ። ሞቃዲሾም የሶማሊያ ዋና ከተማ ሆነች “
ይሁን እንጂ ሁለቱ ሶማሌዎች በተዋሃዱበት ወቅት ጠቅላይ ሚንስቴር የተመረጠው ከአሁኗ ሶማሊላንድ ቢሆንም ነገር ግን በዙሪያው የተሰበሰቡት ካቢኔ የሞቃዲሾ ሰወች ስለነበሩ ግንኙነቱ እየተባላሸ መጣ፡፡ከጄኔራል ዚያድ ባሬ ጋር በነበረው ቅሬታም ጄኔራል ሞርጋንን በመላክ ሶማሊላንድን ለማንበርከክ ቢሞከርም የሶማሊላንድ ህዝብ ታግሎ ነፃ ወጣ፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ሶማሊላንድ የሀገርንት እውቅና ዳግም ባይሰጣትም De facto state ሆና ኖራለች! ሁለቱ ሶማሌዎች እንደ ሀገር በጋራ ከሚያገናኛው ጉዳዮች አንዱ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሲሆን በአሁን ሰኣት እነዚህ የምክር ቤቱ አባላት ለቀው እየወጡ እንደ ሆነ ይሰማል፡፡
ኢትዮጵያ ባላት የባህር በር እና የወደብ ፍላጎት መሠረት ከሶማሊላንድ ጋር የመግባቢያ ሰነድ መፈራረሟ ይታወቃል፡፡ ይህንንም ተከትሎ ሶማሊያ ሉዓላዊ መብቴ እና ክብሬ ተነኳቷል በማለት በቀጣነው እና በአለም አቀፍ መህበረሰብ ፊት ፕሬዝዳንታቸው ሀሰን ሼህ ማህሙድ ግልቢያ ጀመሩ፡ ግልቢያቸው ደስታ ያልሰጣቸው የቱርኩ ጠቅላይ ሚንስቴር ኢትዮጵያን እና ሶማሊያን በእስታንቡል በመጋበዝ ሽምግልና ተቀመጡ፡ ቀንቶአቸውም ሁለቱ ሀገራት የአንካራ የሰላም ስምምነት ተፈራረሙ- ከሶማሊላንድ ጋር የተገባውም የመግባቢያ ሰነድ ጉዳይ ከዚያ ወዲህ ተቀዛቅዞ በዝምታ ቆየ፡፡
በሰሞኑ እስራኤል በጠቅላይ ሚንስቴሯ ቤንጃሚን ኔታንያሁ አማካኝነት ለሶማሊላንድ የሀገርነት እውቅና ሰጠች፡፡ እውቅናውንም ተከትሎ የአለም ሀገራት መበሁት ጎራ እየተከፈሉ የሚገኙ ይመስላል፡፡ አብዛጮቹ ወዲያውኑ ውሎ ሳያድር የተቃውሞ ድምጽ ማሳመት ጀመሩ፡፡ ቱርክ፡ ሶማሊያ፤ ጂቡቲ፤ ኤርትራ እና የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ወዲያውኑ ተቃውሞአቸውን አሰሙ፡ ቻይናም ዘግታ ከተቃውሞ ጎራ ተቀላቀለች፡፡ እጅግ የሚጠበቁት አሜሪካ እና ኢትዮጵያ ዘገዩ፡፡ በአስተመጨረሻ አሜሪካ ሶማሊላንድ ማን ናት፡ ካሉ በኃላ ግድ የለም ይደርሳል በማለት ነገሩን በአጭሩ ቀጩት፡፡ ኢትዮጵያ ይህ ጽሁፍ እስከተፃፈበት ጊዜ ድረስ አቋሟን አልገለፀችም፡፡ ደቡብ ሱዳን ደግሞ እውቅና ለመስጠት ዝግጅት ላይ ነኝ ጠብቁኝ ብላለች፡፡ ምናልባትም የኢትዮጵያ ፓርላማ ነገ ታህሳስ 21 ቀን 2018 ዓ/ም በሚኖረው ስብሰባ አንድ ነገር ማለቱ ይቀራል?
እንደ እኔ ሀሳብ ግን በቆራጥነት አውቅናውን ለሶማሊላንድ በመስጠት የባህር በሩን እና የወደብ ጥቅሙን በማስከበር፡ በቀጠናው ላይ ያለውን ተጽዕኖ በማጉላት ግብጽን ከቀጠናው እንታፈገፍግ በማድረግ የራሱ ወደ ሆነው የአሰብ ወደብ እና የባህር በር ጉዞውን ከህዝቡ ጋር መቀጠል አለበት ብዬ አስባለሁ፡፡
ቸር ያሰማን!
ባሻ ት.
ሀገር ማለት … ?
ሀገራት ስለሀገር ትርጉም እና ምንነት ለመግለጽ እስከ አሁን ከሞንቴ ቪዲዮ ኮንቬንሽን (Monte Video Convention On the Right and duties of States: 26 December 1933) የተሻለ ሰነድ አለ ለማለት እቸገራለሁ
በዚህ በሞንቴቪዶ የቃል ኪዳን ሰነድ ውስጥ ሀገር እንደ አንድ አለም አቀፍ የሕግ ሰውነት እንዳለው አካል አረት መሠረታዊ ጉዳዮችን መያዝ እንዳለባት ተደንግጎ ይገኛል፡፡ በቃል ኪዳኑ አንቀጽ አንድ መሠረት ሀገር በአለም አቀፍ ህግ የህግ ሰውነት የሚኖረው ቋሚ ህዝብ፤የተወሰነ ድንበር ወይም ወሰን፤መንግስት እና ከሌሎች ሀገራት ጋር ህጋዊ ስራዎችን ለመስራት ብቁ ሲሆን ነው ይላል፡፡
ሀገር ማለት ከላይ እንደ ተገለፀው ህዝብ፤ ድንበር/ግዛት፤ መንግስት እና ከሌሎች ሀገራት ጋር የመስራት ህጋዊ ብቃት ከሆነ እውቅና (Recognition) ለምን አስፈለገ? ይኸው በመግቢያው የተገለፀው የሞንቴቪዶ ቃልኪዳን ሰነድ ሀገር ያለ እውቅና መቆም ትችላለች ይለናል በአንቀጽ ሦሥት ስር፡፡
“The political existence of the state is independent of recognition by the other states. Even before recognition the state has the right to defend its integrity and independence, to provide for its conservation and prosperity, and consequently to organize itself as it sees fit, to legislate upon its interests, administer its services, and to define the jurisdiction and competence of its courts.”
የአንድ ሀገር ህልውና በሌላ ሀገር እውቅና ላይ የተመሠረተ አይደለም፡፡ ከእውቅናም በፊት አንድ ሀገር ሉዓላዊነቱን እና ነፃነቱን የማስከበር፤ለብልጽግና እና እድገቱ መጠበቅ፤እና በዚህም መሠረት ይሆናል ባለው መልክ እራሱን የማደራጀት፤ጥቅሞቹን በህግ መደንገግ እና አግልግሎቶቹን ማስተዳደር እና የፍርድ ቤቶቹን ፍቅደ ስልጣንና ብቃት መደንገግ ይችላል ወይም የመወሰን መብት አለው፡፡
የሶማሊላንድ ሀገርነት እና የሰሞኑ የእስራኤል የሀገርነት እውቅና
ይህ ከሆነ ታዲያ ለአንድ ሀገር እንደ ሀገር መቆጠር እውቅና ለምን አስፈለገ? ሶማሊላንድ ሀገር አይደለችም? የሀገርነት እውቅና ለምን አስፈለጋት?
ሶማሊላንድ በእንግሊዝ ቅኝ ግዛት ስር የነበረች እና ነፃነቷን እንደ ማንኛውም የአፍሪካ ሀገሮች ከተጎናፀፈች በኃላ በጣሊያን ሶማሊላንድ ወይም ከዛሬዋ ሶማሊያ ጋር በSomali Youth League እንቅስቃሴ ስር ታላቋን ሶማሌ ለመመስረት መቀላቀሏን ከተፃፉ ታሪኮች መረዳት ይቻላል፡፡ እውቁ የኢትኖግራፊ ፀሐፊ አፈንዲ ሙተቂ እንዲህ በማለት በማህበራዊ ሚዲያ ገፁ ለጥፎ አግኝቻለሁ፡፡
“ እንግሊዝ በ1880 ገደማ የአሁኑን የሶማሊላንድ ግዛት በወረራ ያዘችውና "British Somaliland" አለችው። ኢጣሊያ ደግሞ በ1890 ገደማ ከቦሳሶ እስከ ኪስማዮ ያለውን መሬት ያዘችና "Italian Somaliland" አለችው። በእነዚህ ግዛቶች ዘመናዊ ቅርጽ ያላቸውና የተደራጁ የቅኝ ግዛት መንግሥታት ተፈጠሩ።
ሁለቱ ግዛቶች በዚህ ሁኔታ ከሰባ ዓመታት በላይ ካሰለፉ በኋላ በ1961 ነፃነታቸውን ተቀዳጁ። ለሁለቱ ግዛቶች ነፃ መውጣት ትልቅ ትግል ያደረገው "Somali Youth League" የሚባል ድርጅት ነው።
ይህ ሊግ በሁለቱም ግዛቶች ቅርንጫፎች ነበሩት። ከዓላማዎቹ አንዱ የተበታተኑትን የሶማሊያ ግዛቶች አንድ ላይ ማሰባሰብ የሚል ነው። በመሆኑም ግዛቶቹ ነፃነታቸውን በሚያገኙበት ዋዜማ ላይ "አንድ መሆን አለብን" የሚል ጥያቄውን አጦዘው።
ሶማሊላንድ June 26/1960 ነፃነቷን ተቀዳጀች። ይህ ነፃነቷ ለአምስት ቀናት ብቻ ቢቆይም 35 ሀገራት (ግብጽ፣ ሊቢያ እና ኢትዮጵያን ጨምሮ) እውቅና ሰጥተዋል። የኢጣሊያ ሶማሊላንድ ደግሞ ከአምስት ቀን በኋላ (July 1/1960) ነፃ ወጣች። በስድስተኛው ቀን በሁለቱ ሀገራት ጠንካራ መሠረት የነበረው Somali Youth League የሰሜኑን ክፍል (ሶማሊላንድ) ተወካዮቹን በጥድፊያ ወደ ሞቃዲሾ አምጥቶ ሶማሊያ አንድ ሀገር መሆኗን አወጀ። ሞቃዲሾም የሶማሊያ ዋና ከተማ ሆነች “
ይሁን እንጂ ሁለቱ ሶማሌዎች በተዋሃዱበት ወቅት ጠቅላይ ሚንስቴር የተመረጠው ከአሁኗ ሶማሊላንድ ቢሆንም ነገር ግን በዙሪያው የተሰበሰቡት ካቢኔ የሞቃዲሾ ሰወች ስለነበሩ ግንኙነቱ እየተባላሸ መጣ፡፡ከጄኔራል ዚያድ ባሬ ጋር በነበረው ቅሬታም ጄኔራል ሞርጋንን በመላክ ሶማሊላንድን ለማንበርከክ ቢሞከርም የሶማሊላንድ ህዝብ ታግሎ ነፃ ወጣ፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ሶማሊላንድ የሀገርንት እውቅና ዳግም ባይሰጣትም De facto state ሆና ኖራለች! ሁለቱ ሶማሌዎች እንደ ሀገር በጋራ ከሚያገናኛው ጉዳዮች አንዱ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሲሆን በአሁን ሰኣት እነዚህ የምክር ቤቱ አባላት ለቀው እየወጡ እንደ ሆነ ይሰማል፡፡
ኢትዮጵያ ባላት የባህር በር እና የወደብ ፍላጎት መሠረት ከሶማሊላንድ ጋር የመግባቢያ ሰነድ መፈራረሟ ይታወቃል፡፡ ይህንንም ተከትሎ ሶማሊያ ሉዓላዊ መብቴ እና ክብሬ ተነኳቷል በማለት በቀጣነው እና በአለም አቀፍ መህበረሰብ ፊት ፕሬዝዳንታቸው ሀሰን ሼህ ማህሙድ ግልቢያ ጀመሩ፡ ግልቢያቸው ደስታ ያልሰጣቸው የቱርኩ ጠቅላይ ሚንስቴር ኢትዮጵያን እና ሶማሊያን በእስታንቡል በመጋበዝ ሽምግልና ተቀመጡ፡ ቀንቶአቸውም ሁለቱ ሀገራት የአንካራ የሰላም ስምምነት ተፈራረሙ- ከሶማሊላንድ ጋር የተገባውም የመግባቢያ ሰነድ ጉዳይ ከዚያ ወዲህ ተቀዛቅዞ በዝምታ ቆየ፡፡
በሰሞኑ እስራኤል በጠቅላይ ሚንስቴሯ ቤንጃሚን ኔታንያሁ አማካኝነት ለሶማሊላንድ የሀገርነት እውቅና ሰጠች፡፡ እውቅናውንም ተከትሎ የአለም ሀገራት መበሁት ጎራ እየተከፈሉ የሚገኙ ይመስላል፡፡ አብዛጮቹ ወዲያውኑ ውሎ ሳያድር የተቃውሞ ድምጽ ማሳመት ጀመሩ፡፡ ቱርክ፡ ሶማሊያ፤ ጂቡቲ፤ ኤርትራ እና የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ወዲያውኑ ተቃውሞአቸውን አሰሙ፡ ቻይናም ዘግታ ከተቃውሞ ጎራ ተቀላቀለች፡፡ እጅግ የሚጠበቁት አሜሪካ እና ኢትዮጵያ ዘገዩ፡፡ በአስተመጨረሻ አሜሪካ ሶማሊላንድ ማን ናት፡ ካሉ በኃላ ግድ የለም ይደርሳል በማለት ነገሩን በአጭሩ ቀጩት፡፡ ኢትዮጵያ ይህ ጽሁፍ እስከተፃፈበት ጊዜ ድረስ አቋሟን አልገለፀችም፡፡ ደቡብ ሱዳን ደግሞ እውቅና ለመስጠት ዝግጅት ላይ ነኝ ጠብቁኝ ብላለች፡፡ ምናልባትም የኢትዮጵያ ፓርላማ ነገ ታህሳስ 21 ቀን 2018 ዓ/ም በሚኖረው ስብሰባ አንድ ነገር ማለቱ ይቀራል?
እንደ እኔ ሀሳብ ግን በቆራጥነት አውቅናውን ለሶማሊላንድ በመስጠት የባህር በሩን እና የወደብ ጥቅሙን በማስከበር፡ በቀጠናው ላይ ያለውን ተጽዕኖ በማጉላት ግብጽን ከቀጠናው እንታፈገፍግ በማድረግ የራሱ ወደ ሆነው የአሰብ ወደብ እና የባህር በር ጉዞውን ከህዝቡ ጋር መቀጠል አለበት ብዬ አስባለሁ፡፡
ቸር ያሰማን!
ባሻ ት.
Send a message to learn more