04/09/2026
ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም
============
የእኖር ወረዳ ምክር ቤት የመኖሪያ ቤት ችግር ውስጥ ለነበሩ ተጋላጮች የቤት ግንባታ አከናውነዋል።
ድጋፍ የተደረገላቸው በወረዳው የሁረድ ቀበሌ ነዋሪ ለሆኑት ተጋላጭ ለወ/ሮ ዘይነባ ሙዘሚልና አሰን ፎያት ናቸው።
በዚህ መልካም ተግባር ላይ የተገኙት የወረዳው የመንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ አበበ አገዘ በወረዳው ሰው ተኮር የብልፅግና ፓርቲ እሳቤ በተለያዩ የበጎ ፍቃድ አገልግሎቶች በተግባር እየተረጋገጠ እንደሚገኝም አመላክተዋል።
አቶ አበበ አክለውም መረዳዳት የማህበረሰቡ ባህል መሆኑን ጠቁመው ይህ መልካም ተግባር የበለጠ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
የወረዳው ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ክቡር አቶ መህዲ አህባብ እንደገለጹት ድጋፉ እንደ ወረዳ "አንድ ተቋም አንድ ቤት" በሚል በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት አቅመ ደካማ ለሆኑ ወገኖች ለማገዝ ያለመ ነው ብለዋል።
ዋና አፈ-ጉባኤው አክለውም የበጎ ፍቃድ አገልግሎት የጽድቅና የነብስ ስራ በመሆኑ ሁሉም የማህበረሰቡን ክፍል በማስተባበር ለሌሎችም ተጋላጭ ወገኖች ተደራሽ ለመሆን መስራት ይገባል ብለዋል።
የወረዳው ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ ፈቲያ ዮሐንስ በበኩላቸው ለዚህ መልካም ስራ መንግስት የተቻለውን ሁሉ እያረገ ቢሆንም የወረዳው ማህበረሰብና የከተማ ነዋሪዎች የጀመሩትን ድጋፋ አጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ብለዋል።
የድጋፉ ተጠቃሚ የሆኑት ወ/ሮ ዘይነባ ሙዘሚልና አቶ አሰን ፎያት ምንም አይነት ጧሪና ደጋፊ የሌላቸው መሆኑን አስረድተዋል።
ቤታቸው አርጅቶ ስለነበር ሁሌ ክረምት ሲመጣ ያሳስባቸው እንደነበር አስታውሰው አሁን ቤት እየተሰራላቸው በመሆኑም እጅግ መደሰታቸውን ገልጸዋል።
ተግባሩ እንዲሳካ ላደረጉ ለቀበሌው ደጋፊ አመራር ለወ/ሪት መሰረት ሀይሌ፣ለወረዳው ምክር-ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ለክቡር መህዲ አህባብና ለምክትል አፈ-ጉባኤ ለክብርት ወ/ሮ ፈቲያ ዮሐንስ፣ለተቋሙ ሙያተኞች፣ለቀበሌው አመራሮችና ማህበረሰብ ከልብ አመስግነዋል ሲል የዘገበው የወረዳው መ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት ዘግቧል።